In Loving Memory · መታሰቢያ

የቀኝ ጌታ አባ መዝሙር ሐዋዝ ጥሩነህ

1912 – 2018 ዓ.ም

በእምነት፣ በፍትህ እና በቤተሰብ ቅርስ የተሞላ ምዕተ ዓመት

Portrait of Kegn Geta Aba Mezmur Hawaz in a blue cloak

የአባታችን ቡራኬ

"እንዴት ሰንብታችኋል? ደህና አርፋችኋል? ቤታችሁ ውስጥ ሁሉም ሰላም ነው? እኔ ደግሞ ደህና ነኝ፣ እግዚአብሔር ይመስገን። እግዚአብሔር ሁላችሁንም ይጠብቅ። ጌታ መድኃኒዓለም ይባርካችሁ፣ ይምራችሁ፣ ረጅም ዕድሜ ይስጣችሁ። አሜን። እግዚአብሔር ሲፈቅድ እንገናኝ።"

— አባ መዝሙር ሐዋዝ

The Extraordinary Life

ታሪካቸው

I

ልደት እና ቅዱስ መነሻ

የቀኝ ጌታ አባ መዝሙር ሐዋዝ የዜማ ቃላት እና ታሪካዊ ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ከነበሩት ከአባታቸው ሊቀ ማዕምራን ሐዋዝ ጥሩነህ እና ከእናታቸው እማሆይ አጠናሽ ተበጀ ታህሳስ 19/1912 ዓ.ም በጎንደር ከተማ ግምጃ ቤት ማርያም ቤተክርስቲያን ግቢ ተወለዱ።

II

የመንፈሳዊ ዕውቀት ጉዞ

ዕድሜያቸው ለትምህርት ሲደርስ ከፊደላት እስከ መዝሙረ ዳዊት ድረስ በግምጃ ቤት ማርያም ተምረዋል። ከመምህር ዜናዊ ውዳሴ ማርያምን፣ አንቀጸ ብርሃን፣ መልክአ ማርያምና መልክአ ኢየሱስን ተምረዋል። ከመምህር ገብረኢየሱስ አቋቋም ተምረው በአቡነ ሚካኤል ሲመተ ዲቁና ተቀብለዋል። ከመምህር ገብረሥላሴ ቅኔ ተምረው የቀኝ ጌታነት ማዕረግን አግኝተዋል።

III

የፍትህ አርበኛ

በ1950 ዓ.ም ላይ በጠቅላይ ፍርድ ቤት የዳኝነት ስልጠና የወሰዱ ሲሆን በጎንደር ከተማ የአጥቢያ ዳኛ ሆነው ሰርተዋል። በጠበቃነት ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል። በጎንደር ከተማም የጠበቆች ማህበር አባል ነበሩ።

IV

ሥርዓተ ምንኩስና

ከእማሆይ እመቤት አስካለ ጋር ቅዱስ ጋብቻ መስርተው ሲኖሩ ከቆዩ በኋላ ህዳር 21/2003 ዓ.ም በወቅቱ የጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ ሥርዓተ ቡራኬና ምንኩስና ተፈጽሞላቸዋል። ሳይታወኩ አርጅተው ቀሪ ዘመናቸውን በፀሎት፣ በፆም እና በምስጋና ያሳልፉ ታላቅ አባት ነበሩ።

V

ሰላማዊ መሰናበት

የሚያርፉበትን ቀን አውቀው ግንቦት 7 ቀን መቼ ነው ብለው ጠይቀው፣ በተወለዱ በ106 ዓመታቸው ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ.ም ያለምንም ስቃይና ህመም ማለዳ በረድኤት ቆይተው ወደ ጌታቸው አርፈዋል።

1912 — 2018

የሕይወት ዘመን

  1. 1912 ዓ.ም

    በጎንደር ተወለዱ

    ታህሳስ 19 በግምጃ ቤት ማርያም ቤተክርስቲያን ግቢ።

  2. Early Years

    መንፈሳዊ ዕውቀት

    ከሦስት መምህራን ተምረው፤ በአቡነ ሚካኤል ዲቁና ተቀብለዋል።

  3. የቀኝ ጌታ ማዕረግ

    ቅኔን ተምረው የቀኝ ጌታነት ማዕረግ ተሰጥቷቸዋል።

  4. 1950 ዓ.ም

    የሕግ ሕይወት

    በጠቅላይ ፍርድ ቤት ሥልጠና ወስደው ከ30 ዓመታት በላይ አገልግለዋል።

  5. 2003 ዓ.ም

    ሥርዓተ ምንኩስና

    ህዳር 21 ከእማሆይ እመቤት አስካለ ጋር በአቡነ ኤልሳዕ ሥርዓተ ምንኩስና ተፈጽሟል።

  6. 2018 ዓ.ም

    ሰላማዊ መሰናበት

    ግንቦት 7 በ106 ዓመታቸው ያለ ስቃይ አርፈዋል።

Aba Mezmur Hawaz with family

የዘላለም ቅርንጫፍ

የቤተሰብ ቅርስ

ልጆቻቸውን በሙሉ አስተምረው፣ አሳድገው፣ አጋብተው ለወግ ማዕረግ ያበቁ የተወደደ አባት፣ አያትና ቅድመ-አያት ነበሩ።

የቤተክርስቲያን መታሰቢያ

የደብረ ግምጃ ቤት ማርያም ድምፅ

የመህለት ጥልቅ ምስጋናዎች አባ መዝሙር ሲጠብቁት የኖሩትን ትውፊት ያሰማሉ።

"ማርያም… እመ አምላክ… ንባርክኪ…"

የሚንቀሳቀሱ ትዝታዎች

በራሳቸው ህያውነት

የተጠበቁ አጭር ቅጽበቶች — ድምፃቸው፣ ቡራኬያቸው፣ ጸጥ ያለ ግርማቸው።

ከአለቃ ጌታ አባ መዝሙር ሐዋዝ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ — በራሳቸው ድምፅ።
በቀብር ሥነ ሥርዓቱ ላይ የቀረበ መታሰቢያና የሕይወት ታሪክ ንባብ።

የአባታችን የቀኝ ጌታ አባ መዝሙር ሐዋዝን ነፍስ ፈጣሪ በቀኙ ያድርግልን ዘንድ እንመኛለን። አሜን።

— በፍቅር፣ ቤተሰቦቻቸው